Friday, September 16, 2011

የኢጣልያ ምርኮኞችና ስለ እነሱ የተደረገ ስምምነት


  • Error loading feed data.

የኢጣልያ ምርኮኞችና ስለ እነሱ የተደረገ ስምምነት

E-mailPrintPDF
User Rating: / 2 http://www.ethiopianreporter.com/pre-rep/index.php?option=com_content&view=article&id=1382:2010-03-03-11-42-35&catid=103:2009-11-13-13-46-23&Itemid=576
PoorBest 
ንጉሠ ነገሥት ምኒልክ የተማረኩ የኢጣሊያ ጦር ምርኮኞች እንዳይገደሉ፤ ወይም ያለወገን በሆነ ዓይነት ሠራዊታቸው እንዳያጉላላቸው አወጁ፡፡ ወደ መናገሻ ከተማቸው ዙሪያ አምጥተውም በምግብ እንዳይጎዱ ከምሪት አስቀመጧቸው፡፡ በተቻላቸው መጠንም የታረዘውን አለበሱት፡፡ በኢጣልያ አገር ሠራዊታቸው በጦርነቱ ድል ከመሆኑ ይልቅ፤ ምርኮኛውን የሚገጥመው ዕድል ሽብር አመጣ፡፡

ምርኮኞቹ የዓድዋ ድል ከተገኘበት ከ (1888 ዓ.ም". የካቲት 23 ቀን አንስቶ እስከ ጥቅምት 19 ቀን 1989 ዓ.ም. ድረስ ቆይተው ከ8 ወር በኋላ ውጫሌ ላይ በ1881 ሚያዝያ 25 ቀን የተደረገው ውል ፈጽሞ መፋቁን ኢጣልያ አወቀችና የምርኮኞቹን መለቀቅ ተስማሙበት፡፡ ይህም በሰደደችው ልዩ መልዕክተኛ በሜጀር ናራዚኒ ተረጋገጠ፡፡
በአጤ ምኒሊክና በኢጣልያ መካከል አዲስ የስምምነት ውል ተደረገ፡፡

*    *    *   
አነፍናፊ አይጦች

አንዳንድ ሰዎች አይጥ ሲያዩ በጣም ይፈራሉ፡፡ የፍራቻቸውን ምክንያት ግን ከነሱ በስተቀር የሚያውቅ ያለ አይመስልም፡፡ አይጥ ከማስፈራቷና ከጉዳቷ ይልቅ ለሰው ልጅ ጥቅሟ ያመዝናልና፡፡

አይጥ ለሰው ልጆች የተለያዩ በሽታዎችን ለመፈወስ የሚያስችሉ መድኃኒቶችን ለመሞከሪያነት ለበርካታ ዓመታት እያገለገለች ትገኛለች፡፡ በቅርቡ በቤልጅግ የተደረገው ሙከራ አይጦች የበርካታ የዓለማችን አገሮች ችግር የሆነውን የተቀበረ ፈንጂ ለማምከን ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳላቸው አረጋግጧል፡፡

በአሁኑ ወቅት አገራችንን ጨምሮ በዓለማችን 69 ሀገሮች ከ60 ሚሊዮን በላይ የተቀበሩ ፈንጂዎች ይገኛሉ፡፡ ለዚህም በመፍትሄነት እ.ኤ.አ በ1990ዎቹ ከአፍሪካ የተወሰዱት ተለቅ ተለቅ ያሉ አይጦች ከፍተኛ አስተዋፅኦ ሊኖራቸው እንደሚችል የጥናት ቡድኑ ኃላፊ ዊት ጆንስ ገልፀዋል፡፡

ቀደም ሲል በተለያዩ ሀገሮች የተቀበሩ ፈንጂዎችን ለማፈላለግ ውሾች ሥራ ላይ ይውሉ እንደነበር የጠቆሙት ዊት ጂንስ፣ ለዚህ ሥራ ከውሾች ይልቅ አይጦችን ማሰልጠን ይቀላል ብለዋል፡፡ በዋነኛነት አይጦች ክብደታቸው ቀላል በመሆኑ የሚያገኙት ፈንጂ ላይ ቢወጡ እንኳን አያፈነዱትም፡፡ አይጦቹን ለዚህ ተግባር ለማራባትና ለማሳደግ የሚያስፈልገው ወጪ በጣም ርካሽ ከመሆኑም በላይ፣ በርካታ ፈንጂዎች በተቀበሩባቸው የትሮፒካል የአየር ንብረት ባላቸው አካባቢዎች መኖር የሚችሉ ናቸው፡፡

(ስነምግባር 2001 ዓ.ም)

*    *    *   
እቴጌ ተዋበች 

ዐፄ ቴዎድሮስ ሸዋን ሁለተኛ ድል አድርገው ሹመቱን በኋላ ለከዷቸው አቶ በዛብኽ መርቀው ወደ በጌምድር እንደ ተመለሱ የሚወዷቸው ባለቤታቸው ክፉውንና ደጉን መከራውንና ደስታውን ሲካፈሏቸው የኖሩት ይልቁንም በተናደዱና በተበሳጩ ጊዜ መክረው የሚያበርዷቸውና የሚያጽናኗቸው እቴጌ ተዋበች በጽኑ ሕመም ታመው ወደቁ፡፡ ዐፄ ቴዎድሮስም ያየር መለወጥ የሚያሽል መስሏቸው ወደ ወረ ይመኑ አመጧቸው፡፡ ነገር ግን ለሰው ተወስኖ ከተሰጠው ዕድሜ ካለቀ በኋላ ያየር መለወጥ የሐኪም ዕውቀት የዘመድም ብዛት የዘርም ታላቅነት ሊያድን አይችልምና ሞቱ፡፡ ዐፄ ቴዎድሮስም ሬሳቸውን በሣጥን አድርገው ወደ ግሼን ለመቅበር ተጓዙ፡፡

እቴጌ ተዋበች ዐፄ ቴዎድሮስን ገና ልጅ ካሳ ሲባል ካገቧቸው አንስቶ ሞት እስኪለያያቸው ድረስ ካገጠባቸው አልተለዩም፡፡ ዕድላቸውም ከባላቸው ጋር የተያያዘ በመሆኑ ዐፄ ቴዎድሮስ ካያታቸው ከእቴጌ መነን ወይም ካባታቸው ከራስ ዐሊ በተዋጉ ጊዜ ላባታቸውና ላያታቸው አድልተው ካፄ ቴዎድሮስ አልተለዩም፡፡ ከዚህ ቀደም ዳዊት ለመንግሥቱ ሲል ከጉልበቱ ከወጣው ልጁ ከአቤሴሎም ጋር ተዋግቷል፡፡ ዐፄ ዮሐንስም ለመንገሥ ዐፄ ተክለ ጊዮርጊስን ወግተው ከማረኩ በኋላ ያለርኅራኄ አስረው ለሞት ሲያደርሷቸው የእኅታቸው ባል መሆናቸውን እግምት ውስጥ አግብተው ሊያመዛዝኑት እንዳልቻሉ እንደዚሁም እቴጌ ተዋበች የባላቸው ክብር የራሳቸው በመሆኑ ካባት ከናታቸው ክብር አብልጠው ለባላቸው ያደሉ ነበር፡፡

(ተክል ጻድቅ መኩሪያ፣ ከዐፄ ቴዎድሮስ እስከ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ፣1961)

*    *    *   
የቄሱ ትንቢት 

"ምነው አባ" ለምንድነው እንደዚህ አፍጥጠው ፊቴን የሚያዩት?" በማለት የሰባት ዓመቷ ሜሪ ሮዝ ጆሲፊን የወደፊት ዕድል የተደነቁት ኮከብ ቆጣሪ ቄስ "ይህ የማይታመን ነው" በማለት አጉረመረሙ፡፡ "ቢሆንም ኮከቧ የሚተነብየውን ልነግራት ይገባል" አሉና ለጆሲፊን "የፈረንሳይ ንግሥተ ነገሥት ተብለሽ ዘውድ ትጭኛለሽ፤ ከባልሽም ጎን በዙፋን ላይ ትቀመጫለሽ" አሏት፡፡

እንዲህ አይነቱን ትንበያ ለማመን በርግጥ አዳጋች ነበር፡፡ ምክንያቱም ጆሲፊን ገረድ ነበረች፡፡ አንዲት ገረድ የፈረንሳይ ንግሥተ ነገሥት ለመሆን እንዴትስ ይቻላታል? ጆሲፊን የኮከብ ቆጣሪውን ትንበያ ትርጉም ለመገንዘብ በጣም ጨቅላ ነበረች፡፡ እናትየዋም ኮከብ ቆጣሪው የተናገሩትን ማመን አልቻለችም፡፡ ኮከብ ቆጣሪው ግን በርግጠኝነት "የኔ ጥረት አንቺን ማስደሰት ወይንም አንቺን ማጭበርበር አይደለም፡፡ በትንበያዬ ብትከፊ ባትከፊ ደንታ የለኝም፡፡ የምናገረው እውነቴን ነው፡፡ የምገልፅልሽ ልደርስበት የቻልኩትን ሀቅ ነው፡፡ ልጅሽ ንግሥት ትሆናለች፡፡ ይሁንና እስከሕይወቷ ፍጻሜ ንግሥት ሆና አትቆይም" አሉ፡፡

ሉዊስ አስራ ስድስተኛ መላውን ፈረንሳይ አሸንፈው የቦርቦ ሥርወ መንግሥት በፈረንሳይ ይቀጥል ዘንድ ከሚወዷትና ከቆንጆዋ ሚስታቸው ከንግሥት ሜሪ አንቶኔቲ ወንድ ልጅ ወለዱ፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ በፈረንሳይ የባህር ማዶ አስተዳደር ሥር የምትተዳደረውና በምዕራብ ኢንዲስ የምትገኘው የማርቲኒኩዊ ደሴት መስፍን የቤት ሠራተኛውን አግብቶ ጆሲፊን ተወለደች፡፡ በኮከብ ቆጣሪው ቄስ ትንበያ መሰረት የንጉሱ የሉዊስ የመጀመሪያ ልጅ ጆሲፊንን አግብቶ ወደዙፋኑ ይዟት ይወጣል፡፡ እንዲህ ዓይነቱ ትንቢት ለጆሲፊን አባት የማይታመን ፌዝ ነበር፡፡ ጆሲፊን ለአቅመ ሄዋን ስትደርስ አባቷ አሌክሳንደር ቤዮሀርኔስ ለተባለ የፈረንሳይ መስፍን ዳሯት፡፡ ከመስፍኑም ወንድና ሴት ልጆች ወለደች፣ የጆሴፊን ሕይወት ግን በዚህ አልተጠናቀቀም፣ ብዙ ታሪኮች ካለፉ በኋላ የፈረንሳዩ ንጉሠ ነገሥት ናፖሊዮንን አግብታ ንግሥት ሆናለች፡፡

(ሰለሞን ኃይለ ማርያም፣ የታላላቅ ሰዎች እውነተኛ የፍቅር ታሪክ፣1990)

*    *    *   
የቋንቋ ተማሪ ቤት ስለ መከፈቱ

ዳግማዊ ምኒልክ የአውሮጳውያንን ሥልጣኔ በአገራቸው ለማስገባት ብርቱ ምኞት ነበራቸው፡፡ ስለዚህም የቋንቋ ትምህርት ማስተማሪያ ተማሪ ቤት በዋና ከተማው በአዲስ አበባ እንዲከፈት ከወሰኑ በኋላ ባለፈው ዓመት በሰኔ ወር ስለ አስተማሪ ጉዳይ ለእስክንድርያ ፓትርያርክ ለአቡኑ ቄርሎስ አንድ ደብዳቤ ጽፈው ነበር፡፡

ይደረስ ከአቡነ ቄርሎስ፤

በአዲስ አበባ ከተማችን ትልቅ የተማሪ ቤት ማድረግ አስበናል፡፡ ይህንን አሳባችንን አቡነ ማቴዎስ ሰምተው በሀገራችን በግብጽ ብዙ የተማሩ ለማስተማር የበቁ ሰዎች አሉ ቢሉን እርስዎ ወደ አቡነ ቄርሎ ልከው እንዲሰዱልን ያድርጉ ብለን ነግረናቸው ይኸው ጽፈንልዎታልና የአቡነ ማቴዎስን ማኅተም አይተው የሚገኝልዎ እንደሆነ ያለ ትዕግሥት በስልክ በቶሎ ቢያስታውቁን እንወዳለን፡፡ ወደርስዎ መላካችን ከሌላ አገር ከማስመጣት ለትምህርትም ለሁሉም ነገር የሃይማኖት ወንድሞቻችን ቢመጡ ይሻላል ብለን ነው፡፡

ሰኔ 26 ቀን 1898 ዓ.ም. አዲስ አበባ ተፃፈ፡፡
ከዚህ በኋላ ሦስት ግብጻውያን አስተማሪዎች መጥተው በ1899 ዓ.ም በጥር ወር በአዲስ አበባ አንድ ተማሪ ቤት ተከፍቶ ማስተማር ጀመሩ፡፡ የተማሪ ቤቱ ዲሬክተር ሙሴ ሐና ቤይ ሰሊብ ይባላል፡፡

ዳግማዊ ምኒልክ የወደፊት አልጋ ወራሻቸውን ልጅ ኢያሱንና የመኳንንቱን ልጆች እነ ሊቀ መኳስ ብሩን እነ ደጃዝማች ተፈሪ መኮንንን ሌሎችንም ወደ ተማሪ ቤቱ ገብተው እንዲማሩ አደረጉ፡፡ ሌላውም ሰው የጃንሆይን አርአያ በመከተል ልጁን እየላከ ለትምህርት ያስገባ ጀመረ፡፡

ትምህርት ቤቱ የዳግማዊ ምኒልክ ተማሪ ቤት ተብሎ በስማቸው ተሰየመ፡፡ የተከፈተውም የሙሴ ኤልግ መኖሪያ በነበረው ቤት ነው፡ በኋላ ግን ይህ አሁን ያለው የተማሪ ቤቱ ሕንጻ በአቡን ሰፈር አጠገብ በጥሩ ሆኖ ተጀምሮ ተቋቋመ፡፡

(መርስዔ ኀዘን ወልደ ቂርቆስ፣ የሐያኛው ክፍለ ዘመን መባቻ፣ 1999)

*    *    *   
የሰው ልጅ ባዶነት

አወይ የኛ ሀጢያት
የእርካታ ትኩሣት
የስሜት እንስሳት
የስም አዳምነት
የስም ሄዋንነት
የሰው ልጅ ባዶነት
መሠልጠን ተብሎ
መሠይጠን ተይዞ
እድሜ መቁጠር ቀርቶ
ህጻናትን መድፈር ትልቅ ዝና ሆኖ
አባት እንኳ ጨክኖ ከልጁ ሲጠጋ 
ለፍትወተ ስጋ
እርካታን ፍለጋ
ወንድም እህትነት
ቀርቶ እንደዘበት
አሁንማ እንስሳነት
አሁንማ እንስሳነት
ታዲያ ምን ይሰማ
ከዚህ የመረረ
ለጆሮ የሻከረ
ለወሬ የቸገረ
አይ የሰው ባዶነት
የስም አዳምነት
የስም ሔዋንነት
ለእርካታ ነጻነት
የስሜት ባርነት

(ማለዳ፣ ጂማ ዩኒቨርስቲ ኪነ ጥበባት ክከብ፣ 1993)

"""""""////""""""
ገራገር

ሰውየው ራሱን ለመግደል ባደረገው ሙከራ ላደረሰው ጉዳት ቅጣት ተጣለበት


ራሱን ለመግደል በመስኮት የተወረወረው ሩሲያዊ የ7 ዓመት ሴት ልጅ ላይ በመውደቁ ልጅቷ ላይ ላደረሰባት ጉዳት እና ቤተሰቦቿ ላወጡት የህክምና ወጪ ከ45ሺህ ብር በላይ እንዲከፍል ባገሩ ፍርድ ቤት ተፈረደበት፡፡

ሰውዬው ከዘጠነኛው ፎቅ ላይ ተወርውሮ ህፃኗ ላይ ከወደቀባት ጊዜ ጀምሮ ለወራት ያህል ሆስፒታል ስትታከም ቆይታለች፡፡ ሰውየው ለሙከራው የተገፋፋው ቤቱ ውስጥ ከፈታት ሚስቱ ጋር በተፈጠረው አለመግባባት ምክንያት ነበር፡፡

"""""""///"""""""
ቢራ ጠጪውና ሲጋራ አጫሹ ቺምፓንዚ ወደ ፀባይ ማረሚያ ተላከ


የሩሲያው ቺምፓንዚ ከለመደው ቢራ የመጠጣትና ሲጋራ የማጨስ ልምድ ለመፈወስ ወደ ፀባይ ማረሚያ ቤት በእንስሳት ጠባቂዎች አማካኝነት ተላከ፡፡

ይህ ቺምፓንዚ የሰርከስ ትርዒትን ያሳይ የነበረ ሲሆን፣ ተተናኳሽ እየሆነ በመምጣቱ ወደ እንስሳት ማቆያ እንዲዛወር ተደርጓል፡፡ የእንስሳት ማቆያውም የበርካታ ልጆች አባት ለመሆን የበቃበት ቦታ ሲሆን፣ በማርከር መሳልና ሁለት የተለያዩ ድምፆችን ማውጣትንም ተለማምዶበታል፡፡

"""""""////""""""
በ24 ሠዓት ውስጥ አንድን ባንክ ሁለት ጊዜ የዘረፈው ተያዘ


በባንክ ዝርፊያ እስር ቤት ቆይቶ የነበረው ጀርመናዊ ዘራፊ ከተፈታ በአንድ ሣምንቱ አንድን ባንክ በ24 ሰዓት ጊዜ ውስጥ ሁለት ጊዜ በመዝረፋ ተያዘ፡፡

የፖሊስ ቃል አቀባይ እንደተናገሩት የ50 ዓመቱ ዘራፊ ወደ ባንኩ በመሄድ ሽጉጡን ደግኖ "ትናንት እዚህ ነበርኩ እናም ተጨማሪ ገንዘብ ዛሬ እንደገና እፈልጋለሁ" እንዳለ ገልጸዋል፡፡

ይህ ዘራፊ ከስምንት ሺህ ብር በላይ የዘረፈ ሲሆን፣ ባንኩ ውስጥ ተገጥሞ በነበረው ካሜራ አማካኝነት በፖሊስ ታድኖ በሶስት ሰዓታት ጊዜ ውስጥ ተይዟል፡፡ ይህ ሰው በባንክ ዝርፊያ ምክንያት እ.ኤ.አ. በ2002 እና 2004 ዓ.ም ታሥሮ ነበር፡፡

"""""""""///"""""
ዶሮዋ ከተለመደው መጠን በላይ እንቁላል ጣለች


ቁመቱ ዘጠኝ ሴንቲ ሜትር ስፋቱ ደግሞ ሃያ አንድ ሴንቲ ሜትር የሆነ እንቁላል አንዲት ዶሮ እንደጣለች እና ይህም መጠን ከተለመደው የእንቁላል መጠን አራት እጥፍ እደሆነ የዶሮዋ ባለቤት ማርክ ኮርኒሽ ገለፁ፡፡

"ከመደንገጤ የተነሳ ዝይ በስህተት ቦታው ላይ የተገኘ መስሎኝ ነበር" ያሉት ኮርኒሽ፣ የእንቁላሉ ቅርፊት እንደ ወረቀት የሣሣ በመሆኑ መሠነጣጠቅ ጀምሯል፡፡ "ምናልባትም ቶሎ መብላት ሳይኖርብኝ አይቀርም" ብለዋል፡፡ ይህቺ ዶሮ ግፋ ቢል ለአምስተኛ ጊዜ እንቁላል የጣለች ሲሆን፣ የዓለምን ሪከርድ መስበር ግን አልቻለችም፡፡ እስከዛሬ ድረስ የተመዘገበው ትልቁ የዶሮ እንቁላል መጠን አምስት አስኳል ያለውና ቁመቱ 31 ሴንቲ ሜትር፣ ስፋቱ 22.8 ሴንቲ ሜትር፣ ክብደቱ ደግሞ ወደ 340 ግራም የሚጠጋ ነው፡፡

Thursday, September 15, 2011

አርባ አራቱ ታቦታተ ጎንደር http://www.melakuezezew.info/2011_08_01_archive.html

አርባ አራቱ ታቦታተ ጎንደር

መግቢያ
ጎንደር በኢትዮጵያ የመንግሥት ታሪክ ከአክሱምና ላሊበላ ቀጥሎ ትልቋ የመንግሥት ማዕከል ነበረች፡፡ በመንግሥት ማዕከልነት የተቆረቆረችው በአፄ ፋሲል (1624-1660 ዓ.ም) ነው፡፡

ጎንደር የመንግሥት ማዕከል ብቻ ሳትሆን በጊዜው የመንፈሳዊ ትምህርት ማዕከልም ነበረች፡፡ በኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን የመጻሕፍት እና የአቋቋም ትምህርት ይበልጥ የተስፋፋውና በየሀገሩ ያሉ ሊቃውንት በመናገሻ ከተማዋ ጎንደር በነገሥታቱ አማካይነት በመሰባሰባቸው ሲሆን ከዚያን ዘመን ጀምሮ እስከዛሬ ድረስ መንፈሳዊ ትምህርት በስፋት የሚሰጥባት የትምህርት ማዕከል ለመሆን ችላለች፡፡
በአሁኑ ሰዓት በሰሜን ጎንደር በሚገኙ 21 ወረዳዎች ከ2117 ያላነሱ ገዳማትና አብያተ ክርስቲያናት ሲኖሩ በዋና ከተማዋ ደግሞ ከ92 ያላነሱ አብያተ ክርስቲያናት ይገኛሉ፡፡

በአብነት ት/ቤት ረገድም የመጻሕፍት ጉባዔያት፣ የአቋቋም ምስክር፣ የቅኔ አብያተ ጉባዔያት እንዲሁም የዜማ ት/ቤቶች በከተማዋ እና በዙሪያዋ በሚገኙ ወረዳዎች ይገኛሉ፡፡ (ስለአብነት ት/ቤቶች በሚቀጥሉት ጊዜያት እመለስበታለሁ፡፡)

44 የመሆናቸው ምሥጢር
በአሁኑ ሰዓት በከተማዋ ከ92 ያላነሱ አብያተ ክርስቲያናት ቢኖሩም በአብዛኛው ስማቸው ደጋግሞ የሚነሳው የ44ቱ ብቻ ነው፡፡ በተለያየ ጊዜ በተለይም ጎንደርን ከማያውቁት ሰዎች ጋር ባደረኩት ውይይት 44ቱን ታቦታተ ጎንደርን በተመለከተ የተለያየ ግንዛቤ እንዳለ ለመገንዘብ ችያለሁ፡፡
አንዳንዶቹ በመላው ኢትዮጵያ የሚገኙት የአብያተ ክርስቲያናት ታቦታት ስያሜ ብዛት ሲመስላቸው ሌሎቹ ደግሞ በጎንደር በጥምቀት በዓል ወደጥምቀተ ባህር የሚወርዱትን ብቻ ስሉ ይደመጣሉ፡፡ ጎንደር ከተማ እየኖሩም የ44ቱን ዝርዝር በውል የማያውቁ ብዙ ሰዎች ገጥመውኛል፡፡
ጎንደር ደብረብርሃን ሥላሴ ቤተክርስቲያን
አርባ አራቱ ታቦታተ ጎንደር ከቤተ መንግሥቶቹ በተጨማሪ ታሪካዊዋ ጎንደር የምትታወቅበት ቅርስ ነው፡፡ ጎንደር ከተማ በአፄ ፋሲል የመንግሥት ከተማ ከመሆኗ አስቀድሞ የአካባቢው ነዋሪዎች ተክለዋቸው የነበሩ አብያተ ክርስቲያናት ነበሩ፡፡ ለምሳሌ ቀሐ ኢየሱስ፣ አርባዕቱ እንስሳ፣ አበራ ጊዮርጊስ፡፡

ጎንደር የመንግሥት ከተማ ከሆነችበት እስከ ጎንደር ዘመን ማክተሚያ ፈፃሜ መንግሥት አፄ ተክለ ጊዮርጊስ (1772-1777) ድረስ 18 ነገሥታት የነገሱ ሲሆን እነዚህም አብዛኛዎቹ አብያተ ክርስቲያናትን አሠርተዋል፡፡

እንግዲህ 44 የሚባሉት አብያተ ክርስቲያናት ጎንደር የመንግሥት ከተማ ከመሆኗ አስቀድሞ የተተከሉበትን ጨምሮ እስከ ፈፃሜ መንግሥት ተክለ ጊዮርጊስ (1772-1777) ድረስ የተተከሉትን ብቻ ሲሆን ቁጥራቸውም 44 ነው፡፡

ከዚያ ወዲህ ከዘመነ መሣፍንት እስከ አሁን የተተከሉ በርካታ አብያተ ክርስቲያናት ቢኖሩም ከ44ቱ የሚቆጠሩ አይደሉም፡፡ በአጠቃላይ አርባአራቱ ታቦታተ ጎንደር በጎንደር ዘመን በጎንደር ከተማና አካባቢው የሚገኙና የነበሩ 44 አብያተ ክርስቲያናት ጥቅል ስም ነው፡፡
ይህም ማለት አሁን ባለው የጎንደር ከተማ ክልል እና ዙሪያውን በሚገኙ አዋሳኝ የገጠር ቀበሌዎች ለምሳሌ፣ ጠዳ፣ ፈንጠር፣ ብላጅግ፣ ደፈጫ እና በመሳሰሉት ቦታዎች የሚገኙ አጠቃላይ የአድባራት ቁጥር ነው፡፡

በጎንደር ዘመን የነገሡ ነገሥታት
ተ.ቁ
የንጉሡ ስም
ዓመተ ምህረት
የዓመት ብዛት
1
አፄ ሠርጸ ድንግል
1553-1587
34
2
አፄ ያዕቆብ
1587-1594
7
3
አፄ ዘድንግል
1594-1595
1
4
አፄ ሱስንዮስ
1595-1623
28
5
አፄ ፋሲል
1623-1659
36
6
አፄ ዮሐንስ (ፃድቁ)
1659-1674
15
7
አፄ ኢያሱ (አድያም ሰገድ)
1674-1698
24
8
አፄ ተ/ሃይማኖት (ርጉም)
1698-1700
2
9
አፄ ቴዎፍሎስ
1700-1703
3
10
አፄ ዮስጦስ
1703-1708
5
11
አፄ ዳዊት (አድባርሰገድ)
1708-1713
5
12
አፄ በካፋ (መሢህ ሰገድ)
1713-1722
9
13
አፄ ኢያሱ 2
1722-1747
25
14
አፄ ኢዮአስ
1747-1762
15
15
አፄ ዮሐንስ 2ኛ (ዘዋሕድእዴሁ)
1762-1763
1
16
አፄ ተ/ሃይማኖት (መናኔ መንግሥት)
1763-1770
7
17
አፄ ሰሎሞን
1770-1772
2
18
አፄ ተ/ጊዮርጊስ (ፈፃሜ መንግሥት)
1772-1777
5

ተካያቸው
አርባአራቱ ታቦታተ ጎንደር የተተከሉት በነገሥታት፣ በመሣፍንት እና በባላባት ወይም በመንጣሪ ሲሆን በቁጥር ደረጃ በነገሥታት የተሠሩት ይበልጣሉ፡፡
አፄ ፋሲል እና መናኔ መንግሥት ተ/ሃይማኖት ሰባት አብያተ ክርስቲያናት ሲያሰሩ የሀገሬው ሰው ደግሞ 10 አብያተ ክርስቲያናትን እንዲተከሉ አድርጓል፡፡ የአፄ ፋሲል አባት አፄ ሱስኒዮስ አዘዞ ተ/ሃይማኖትን የተከሉ ሲሆን ዳግሚት ደብረሊባኖስ ተብላ በነገሥታቱ ዘመን የዕጨጌው መቀመጫ ይኽው ደብር ነበር፤ የደብሩ አለቃ የማዕረግ ስምም እንደ ደብረሊባኖስ ገዳም ፀባቴ ነው፡፡ አፄ ፋሲልና አፄ ሱስንዮስ የተቀበሩትም በዚሁ ደብር ሲሆን መቼና እንዴት አጽማቸው ፈልሶ እንደሔደ የጽሑፍ ማስረጃ ማግኘት ባልችልም በአሁኑ ሰዓት ግን ከጣና ገዳማት አንዱ በሆነው በዳጋ እስጢፋኖስ የሁለቱ ነገሥታት አጽም ይገኛል፡፡ (ስለ እጨጌ፣ አዘዞ ተ/ሃይማኖት እና ዳጋ እስጢፋኖስ በሌላ ጊዜ እመለስበታለሁ፡፡)
በዳጋ እስጢፋኖስ የሚገኘው የአጼ ሱሲኒዮስ እና የልጃቸው አጼ ፋሲል አጽም

መተዳደሪያቸው
በነገሥታቱ እና በመሣፍንቱ የተሠሩት አብያተ ክርስቲያናት አገልጋዮች ተተክለውባቸው ወይም ተመድበውላቸው ለመተዳደሪያ የአካባቢው ቀበሌ እየተከፋፈለ ይሰጣቸዋል፡፡ ይህም ሪም ይባላል ይህም ማለት የዚያ አካባቢ ነዋሪ በዓመት እህል እየሠፈረ ለካህናቱ መተዳዳሪያ እንዲያመጣላቸው ነገሥታቱ አካባቢያዎቹን እየከፋፈሉ ይሠጣሉ፡፡ ለምሳሌ የአደባባይ ተ/ሃይማኖት ሪም በበለሳ ወረዳ ሰፊ መሬት፣ የአደባባይ ኢየሱስ ሪም በጐርጐራ፣ በቡቻራ፣ በብችኝ፣ በማንጌ፣ በዋርሄ ነበር፤ የአጣጣሚ ሚካኤል ሪም በደንቢያ ነበር፡፡
አካባቢው ነዋሪ እና በባላባት የተተከሉት አድባራት ግን ምዕመናን አሥራት በማውጣት የመቀደሻ ንዋያተ ቅድሳቱን ፤ዕጣን ፤ ጧፍ እና ሌሎችንም ለቤተክርስቲያን በማበርከት አገልግሎት ይሰጡ ነበር ፡፡ ዛሬ በገጠር እንዳሉት ካህናት አብዛኛዎቹ አራሾች እና ገበሬዎች ስለሆኑ እያረሱ የሚቀድሱ፤ እየቀደሱ የሚያርሱ አገልጋዮች ነበሩ ዛሬም አሉ ፡፡

የአድባራት የማዕረግ ስም
እስከ አፄ አድያም ሰገድ ኢያሱ ዘመን የተሰሩት አብያተ ክርስቲያናት የማዕረግ ስም ሳይኖራቸው በተሰሩበት አካባቢ በሚተከሉበት ወቅት ባጋጠመ ክስተት እና በታቦቱ ስም ይጠሩ ነበር፡፡  ለምሳሌ፡- ቀሐ ኢየሱስ፣ አበራ ጊዮርጊስ፣ አባ እንጦንስ፣ ፊት አቦ፣ ግምጃቤት ማርያም
ከአፄ ኢያሱ አድያም ሰገድ በኋላ ግን ለጎንደር አድባራት ሥርዓተ አስተዳደር ወጥቶ ደብሮችን በደረጃ መለየትና የማዕረግ ስም መስጠት ስለተጀመረ በነገሥታት የተሠሩት የማዕረግ ስም እየተሰጣቸው በነበራቸው ላይ ተጨምሮ ይጠሩበት ጀመር፡፡ ለምሳሌ፡- መካነ ነገሥታት ግምጃ ቤት ማርያም፣ ርዕሠ አድባራት አደባባይ ኢየሱስ እና ሌሎችም ፡፡


የአርባ አራቱ ታቦታተ ጎንደር ዝርዝር

ተ.ቁ
የደብሩ ስም
የተካዩ ስም
የደብሩ አለቃ ስም
1
አዘዞ ተ/ሃይማኖት
አፄ ሱስንዮስ
ፀባቴ
2
ፊት አቦ
አፄ ፋሲል
ሊቀ ዲያቆን
3
ፊት ሚካኤል
አፄ ፋሲል
ሊቀ ዲያቆን
4
አደባባይ ኢየሱስ
አፄ ፋሲል
ጽራግ ማሠሬ
5
ግምጃ ቤት ማርያም
አፄ ፋሲል
ሊቀ ማእምራን
6
እልፍኝ ጊዮርጊስ
አፄ ፋሲል
ሊቀ ማእምራን
7
መ/መ/መድኃኔዓለም
አፄ ፋሲል
ሊቀ ማእምራን
8
አቡን ቤት ገብርኤል
አፄ ፋሲል
መልአከ ምህረት
9
ፋሲለደስ
አፄ ሰሎሞን
ሊቀ ድማህ
10
አባ እንጦንስ
ፃድቁ ዮሐንስ
መልአከ ምህረት
11
ጠዳ እግዚአብሔር አብ
ፃድቁ ዮሐንስ
መልአከ አርያም
12
አርባዕቱ እንስሳ
አቤቶ አርምሐ

13
ቀሐ ኢየሱስ
የአገሬው ትክል

14
አበራ ጊዮርጊስ
የአገሬው ትክል

15
አደባባይ ተክለሃይማኖት
አዲያም ሰገድ ኢያሱ
ቄስ አፄ
16
ደብረ ብርሃን ሥላሴ
አዲያም ሰገድ ኢያሱ
መልአከ ብርሃናት
17
ዳረገንዳ ኤዎስጣቴዎስ
አድባር ሰገድ ዳዊት
ሊቀ ጉባዔ
18
አጣጣሚ ሚካኤል
አድባር ሰገድ ዳዊት
መልአከ ገነት
19
ጐንደር ሩፋኤል
አፄ በካፋ
መልአከ ፀሐይ
   20
ደፈጫ ኪዳነ ምህረት
አፄ በካፋ
መልአከ ህይወት
   21
ቅ.ዮሐንስ መጥምቅ
ራስ ወልደ ልዑል
መልአከ ጽጌ
   22
ጐንደር ልደታ ማርያም
አፄ ዮስጦስ
አለቃ
   23
ሠለስቱ ምዕት
አፄ ቴዎፍሎስ
መልአከ ሰላም
   24
ጎንደር በአታ ለማርያም
መናኔ መንግሥት ተ/ሃይማኖት
መልአከ ኃይል
   25
ወ/ነጐድጓድ ዮሐንስ
መናኔ መንግሥት ተ/ሃይማኖት
መልአከ ተድላ
   26
ጐንደር ቂርቆስ
መናኔ መንግሥት ተ/ሃይማኖት
ሊቀ አእላፍ
   27
ጐንደር ሐዋርያት(ጴጥሮስ ወጳውሎስ )
መናኔ መንግሥት ተ/ሃይማኖት
አለቃ
   28
ፈንጠር ልደታ
መናኔ መንግሥት ተ/ሃይማኖት
አለቃ
   29
ሰሖር ማርያም
መናኔ መንግሥት ተ/ሃይማኖት

   30
ወራንገብ ጊዮርጊስ
መናኔ መንግሥት ተ/ሃይማኖት
አለቃ
   31
ምንዝሮ ተ/ሃይማኖት
አፄ ሠርፀ ድንግል
አለቃ
   32
ደ/ፀሐይ ቊስቋም
እቴጌ ምንትዋብ
መልአከ ፀሐይ
   33
ደ/ምጥማቅ ማርያም
ፈፃሜ መንግሥት ተ/ሃይማኖት
ዐቃቤ ሰዓት
   34
አባ ሳሙኤል
ፈፃሜ መንግሥት ተ/ሃይማኖት
አለቃ
   35
ጐንደሮች ማርያም
የአገሬው ትክል
አለቃ
   36
ጐንደሮች ጊዮርጊስ
የአገሬው ትክል
አለቃ
   37
አባ ጃሌ ተ/ሃይማኖት
ደጃች ወንድወሰን
አለቃ
   38
ዐቢየ እግዚእ.ኪ/ምህረት
ራስ ገብሬ

   39
ብላጅግ ሚካኤል
የአገሬው ትክል

   40
አሮጌ ልደታ
የአገሬው ትክል

   41
ጫጭቁና ማርያም
የአገሬው ትክል

   42
ጋና ዮሐንስ
የአገሬው ትክል

   43
ራ ሚካኤል
የአገሬው ትክል

   44
ዳሞት ጊዮርጊስ
የአገሬው ትክል


ጎንደር ደብረብርሃን ሥላሴ ቤተክርስቲያን በስተጀርባ ዕይታ

ከዚህ በላይ ያለው ሠንጠረዥ የ44ቱን ታቦታተ ጎንደር ዝርዝር የያዘ ሲሆን ከ44ቱ አድባራት መካከል በአሁኑ ሰዓት የሌሉ ስድስት ናቸው፡፡
የአድባራቱ የኪነ ሕንፃ ውበት ምን ይመስላል? አድባራቱ ምን ችግር ገጠማቸው? እነዚህ የጠፉት አድባራት እነማን ናቸው? በአሁኑ ሰዓት ባለው የከተማ ክልል የት ቦታ ላይ ይገኙ ነበር ? የሚለውን ጥያቄ ሚቀጥለው ክፍል እንመለከተዋለን፡፡
ይቆየን

18 comments:

Anonymous said...
BERTULIN. AMLAK YABERTACHIHU.
Anonymous said...
BRAVE.KEEP IT UP!!!!!!!!
Anonymous said...
Bewunetu tilik jimaro new fitsamewun yasamirilin !!
Anonymous said...
ዲ.ን መላኩ….ለጽሁፍህ እግዚአብሄር ይስጥልን…የልደታ አለቃ መልዓከ ስብሃት አይደለም እንዴ የሚባለው…አንተ ግን …አለቃ ይባላሉ ብለሃል…በጊዜ ሂደት ተቀይሮ ይሆን እንዴ

ወልደ ኤስድሮስ ዘልደታ
መንግስቴ said...
እስካሁን ከምከታተላቸው ብሎጎች ተጨማሪ ይህን በማዬቴ እጅግ በጣም ደስ ብሎኛል።
እግዚአብሔር ከአንተ ጋር ይሁን። በርታ።
Anonymous said...
I like it ,need to get reporters and and if you include refences(live references too -Abatoch) that will be nice and will be library in the future. Share websites to each other.


http://debelo.org/

http://www.zeorthodox.org/

http://www.melakuezezew.info/

http://www.kesisyaredgebremedhin.com/

http://www.adebabay.com/

http://www.betedejene.org/

http://www.aleqayalewtamiru.org/

http://www.mahletzesolomon.com/

http://degusamrawi.blogspot.com


http://www.tewahedomedia.org

http://www.eotc-mkidusan.org/site/

http://suscopts.org/

http://www.dejeselam.org/

http://mosc.in/
selam said...
omg thanks to God and diacomn melaku kale hiwet yasemalin fitamehn yasamre ageliglothn yibark
selam
u.s.a
Anonymous said...
Thank you for your all your help and I able to know a little bit the gonder spritual and historical facts.
I appreciate the blessed duty which is to promote holy places of Gonder and other parts of the country.
wassie mersha said...
Thank u for this historical post
God bless you
Anonymous said...
I also like www.debelo.org it is one of the wide resource our church need to have.
Anonymous said...
This is a great starting.Let God give you his grace and keep your effort to maintain it. The sight has a good organization and brief message which is an excellent lay out. Let God help you your spirit. I am willing to help in what ever way I can.

Samuel Negash from Chicago USA
Anonymous said...
Oh I have seen lots of blogs today and really feel happy.
Thank u Dn. Melaku, God give u long life.Kele Hiwot yasemaln, gena sintun tasawkun yihon kemalet wuchi min elalehu.

Tesfahun, North America
ፊልጶስ እምቤተ ኤስድሮስ said...
ዉድ ወንድሜ ዲ/ን መላኩ በየሳምንቱ የምትፅፍልን ነገር ታሪክን አንዲሁም ሃይማኖታዊ ትዉፊትን በደንብ እንድንረዳ ስላደረገን አጅጉን ላመሰግንህ አወዳለሁ። በተረፈ ደግሞ መሰረታዊ የቤተክርስቲያናቺን ትምህርቶች ለምሳሌ ስለ አአማደ ቤ/ን ብፅትፍልን የሚል አስተያየት አለኝ አግዚአብሔር ፀጋዉን አብዝቶ ረጅም እድሜን ይስጥልኝ።
teka said...
thanks dn engineer Melaku keep it up by introducing the history of our mom EOTC
GOD BLESS U
Anonymous said...
ዲያቆን መላኩ እግዚያብሄር ያበርታህ።
Anonymous said...
as time passes by those truth preached by our forefathers where on the verge of being forgotten.on our era ,the nation is consumed with western beliefs esp .the past twenty years or so this is being a chronic problem to the existence of we who believe on the truth .beyezemenu amlake hulun ehdeyechelotaw yasenesawalena antefam.EGEZIABEHARE AGELGELOTACHUN YEBAREKAN HULACHENM ENDAN !
Anonymous said...
kalhiwoten yasemalene
Anonymous said...
Best Please keep it up!!