Wednesday, May 8, 2013

ለዓይን እድገት በእርግዝና ወቅት ብርሃን ያስፈልጋል ተባለ
በእርግዝና ወራት ብርሃን ማግኘት ፅንሱ በሚኖረው የአይን እድገት ላይ አዎንታዊ ሚና እንደሚኖረው አንድ ጥናት አመለከተ፡፡ ኔቸር በተሰኘ ጆርናል ላይ የታተመው ጥናት እንደሚያመለክተው የእርግዝና ጊዜያቸውን በጨለማ ውስጥ እንዲያሳልፉ የተደረጉ አይጦች የወለዷቸው ግልገሎች ከሌሎቹ ጋር ሲነፃፀር የማየት አቅማቸው ደካማ ሆኖ ተገኝቷል፡፡ ጥናቱ እንደሚጠቁመው ከዚህ ግኝት በመነሳት ዓይን ውስጥ ለሚገኙ የደምስሮች ዕድገት ብርሃን አስፈላጊ እንደሆነ አመላካች ነው ብሏል፡፡

No comments:

Post a Comment