Wednesday, May 8, 2013


በኢትዮጵያ የወባ ትንኝ መድሃኒቱን መቋቋም በመጀመሯ ኢትዮጵያ ዲዲቲን መጠቀም አቆመች ፡፡ ደቡብ አፍሪቃ ዛሬም ጥቅም ላይ ማዋሏን እንደቀጠለች ነው፡፡ኢትዮጵያ ካለፉት አራት ዓመታት ወዲህ ይህን መድሃኒት መጠቀም ማቆሟን የጤና ጥበቃ ሚኒስትሩ ገልፀዋል። ዲዲቲ መጠቀም እንዲቀር ለዉሳኔ ካደረሱ ምክንያቶች አንዱ የወባ ትንኝ መድሃኒቱን መቋቋም መጀመሯ ነዉ።
የተመድ የህፃናት መርጃ ድርጅት UNICEF በኢትዮጵያ የወባ በሽታ በሚያሰጋዉ አካባቢ የሚኖረዉን ህዝብ ቁጥር ወደ 50 ሚሊዮን እንደሚጠጋ ይገልፃል። በየዓመቱም እስከ ዘጠኝ ሚሊዮን የሚጠጋ ሰዉ በበሽታዉ እንደሚጠቃ ድርጅቱ በድረ ገፁ አስፍሯል። በሀገሪቱ በህፃናት ላይ ከሚደርሰዉ ሞት 2o በመቶዉ በወባ ምክንያት እንደሆነ UNICEF ያትታል።

No comments:

Post a Comment